ኢየሱስ ክርስቶስ “ወደ ፈተናም አታግባን፣ ከክፉ ሁሉ አድነን እንጂ” የሚለውን ጸሎት ሲያስተምረን ድካማችንን እንድንናዘዝ እያስተማረን ነው፣ ያለብንን የመንፈሳዊ ውጊያ፣ እንዲሁም በእግዚአብሔር ላይ ጥገኞች መሆናችን፣ አብ ከፈተና ከልሎ በታማኝነት ጸንተን እንድንገኝ እንዲጠብቀን የጠላታችን ተንኮል እንዳያገኘን እንዲታደገን የቀረበ ጸሎት ነው፤
የይቅርታ ልመናው በእኛ ብቁነት ላይ የተመሠረተ አይደለም። በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በተገለጠው በእግዚአብሔር ምሕረት ላይ የተመሠረተ ነው። እውነተኛ ንስሐ ዝም ብሎ ማዘን ብቻ ወይንም ስለ ራስ ጥሩ ስሜት አለመሰማት አይደለም። በመናዘዝ፣ በትሕትና እና በምሕረቱ በመታመን ወደ አብ መመለስ ነው። የተቀበልነው ምሕረት ሌሎችን ይቅር እንድንል ያስተምራናል፤
ክርስቶስ ማዕከል የሆነበት፣ ቅዱስ ቃሉ የሚሰበክበት፣ ቤተ ክርስቲያን በተልእኮ ያለችበት። Christ-centered. Bible-preaching. Community on mission